ቀን
22.11.2016
ካናዳ የሚገጘዉ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ የግዕዝ ቋንቋ ትምህርት መስጠት እንደሚጀምር ተገለጠ። በዩንቨርሲቲዉ በታሪክ ትምህርት ዘርፍ ዶክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት በቅርብና መካከለኛዉ የምስራቅ ስልጣኔ ትምህርት ክፍል ስር በጎርጎሮሳዊዉ ዘመን ቀምር ከጥር 2017 ጀምሮ ቋንቋዉን ማስተማር ይጀምራል።
በግዕዝ ቋንቋ በርካታ ጥንታዊ የሥነ-ፅሁፍ ፣ የፍልስፍና ፤የሥነ-ክዋክብት እንዲሁም የሕክምና ጹሁፎች በመኖራቸዉ ቋንቋዉን ማጥናት የመካከለኛዉ ዘመንን የሜዲተራንያን ስልጣኔና ታሪክ ላይ ለሚደረገዉ ምርምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለዉ ተብሏል።
ከደቡብ ሴሜቲክ ቋንቋ የሚመደበዉ የግዕዝ ቋንቋ በአክሱም ዘመን ይነገር እንደነበር መዛግብት ይጠቁማሉ ።በጎዕዝ የተፃፉ አበዛኛወቹ መፃህፍት ሀይማኖታዊ ይዘት ያላቸዉ ቢሆኑም የመካከለኛዉ ዘመን ስልጣኔን የሚሳያሳዩ የተለያዩ የስነፅሁፍ፣ የፍልስፍና፤ የህክምናና የስነከዋክብት መፃህፍትም በዚሁ ቋንቋ እንደሚገኙ የዘርፉ ተመራማሪወች ይገልፃሉ። በመሆኑም የመካከለኛዉን ዘመን ታሪክ ለሚያጠኑ ተመራማሪወች አሁን አሁን ቀልብ እየሳበ የመጣ ይመስላል።
በቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ በታሪክ ትምህር ዘርፍ ዶክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ እንደሚናገሩት በቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ የቅርብና የመካከለኛዉ ዘመን ስልጣኔ ትምህርት ክፍል ስር በጎርጎሮሳዊዉ ዘመን ቀመር ከጥር 2017 ጀምሮ የግዕዝ ቋንቋ መስጠት ይጀምራል ።በትምህርት ክፍሉ ከአሁን ቀደም አረብኛና ዕብራይስጥን የመሳሰሉ የሴም ቋንቋወች እየተሰጡ መሆናቸዉን ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ ተናግረዋል።
«ግዕዝ የኢትዮጵያ ጥንታዊ የቤተክርስቲያን ቋንቋ ብቻ አይደለም ። ከአረብኛና ከዕብራይስጥ ጋር ዝምድና ያለዉ አስፈላጊ ቋንቋ ነዉ።
ይህንን ቋንቋ የሚያስተምሩ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ የቅርብና የመካከለኛዉ ምስራቅ ስልጣኔ ትምህርt ክፍል ሰወች አረብኛና ዕብራይስጥም ያስተምራሉ።»
በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ምርምር ያካሄዱት ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ፤ ላቲን በአዉሮፓ ባህልና ቋንቋ ላይ ያለዉን ተፅኖ ያህል ግዕዝም በምስራቅ አፍሪካ ታሪክ ላይ ተፅዕኖ አለዉ ብለዋል። ምንም እንኳ ቋንቋዉ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስቲያን ዉጭ ተግባቦት ላይ እየዋለ ባይሆንም ፣በቋንቋዉ የተፃፉ የመካከለኛዉ ዘመን የሜዲተራኒያንን ታሪክና ስልጣኔ የሚያሳዩ በርካታ ፅሁፎች እንደሚገኙ ገልፀዋል።
« ግዕዝ ቋንቋ የተፃፉ በግዕዝ ብቻ የምናገኛቸዉ ፅሁፎች አሉ። በቀደመዉ ዘመን ወደ ግዕዝ የተተረጎሙ ነገር ግን መሰረታቸዉ የሜዲተራንያኑ አለም የሆኑ የጠፉና በጭራሽ ሊገጉ የማይችሉ ፅሁፎችም አሉ ። እነዚህን ፅሁፎች ለማግኘት ከኢትዮጵያ በስተቀር ሌላ አማራጭ የለም።»
ይሁን እንጅ ግዕዝን ማጥናት በቋንቋዉ የተፃፉ የ2000 አመት እድሜ ያላቸዉን በርካታ ፅሁፎች ላይ ምርምርና ጥናትን ለማድረግ እድል የሚሰጥና ለታሪክ ምርምር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።ይሁን እንጅ ቋንቋዉ ያለዉን ጠቀሜታ ያህል ትኩረት አልተሰጠዉም ። በመሆኑም የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ ይህንን የጥናት ተቋም በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል የማድረግ አላማ እንዳለዉ ጨምረዉ ገልፀዋል።
«በተለየ ሁኔታ ተስፋ የምናደርገዉ እዚህ ቶሮንቶ የከፈትነዉ። የጥናት ተቋም ወደፊት በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል እንዲሆን ነዉ። ያ ነዉ የእኛ አላማ።»
ለጥናት ተቋሙ በካናዳ የሚገኙ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በተለይ ዘ ዊክ ኤንድ በሚባል ቅፅል ስሙ የሚታወቀዉ ድምፃዊ አቤል ተስፋየ በግሉ 50 ሺህ የካናዳ ዶላር ማበርከቱ ታዉቋል።
በጀርመን ሃገር ሃምቡርግ ዩንቨርሲቲ በኢትዮጵያ ጥናቶች ትምህርት ክፍል እየተሰጠ የሚገኘዉ የግዕዝ ቋንቋ፣ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ዉጭ ያለ ሁለተኛዉ ግዕዝን የሚያስተምር ተቋም ይሆናል።
ፀሐይ ጫኔ
አዜብ ታደሰ
ካናዳ የሚገጘዉ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ የግዕዝ ቋንቋ ትምህርት መስጠት እንደሚጀምር ተገለጠ። በዩንቨርሲቲዉ በታሪክ ትምህርት ዘርፍ ዶክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት በቅርብና መካከለኛዉ የምስራቅ ስልጣኔ ትምህርት ክፍል ስር በጎርጎሮሳዊዉ ዘመን ቀምር ከጥር 2017 ጀምሮ ቋንቋዉን ማስተማር ይጀምራል።
በግዕዝ ቋንቋ በርካታ ጥንታዊ የሥነ-ፅሁፍ ፣ የፍልስፍና ፤የሥነ-ክዋክብት እንዲሁም የሕክምና ጹሁፎች በመኖራቸዉ ቋንቋዉን ማጥናት የመካከለኛዉ ዘመንን የሜዲተራንያን ስልጣኔና ታሪክ ላይ ለሚደረገዉ ምርምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለዉ ተብሏል።
ከደቡብ ሴሜቲክ ቋንቋ የሚመደበዉ የግዕዝ ቋንቋ በአክሱም ዘመን ይነገር እንደነበር መዛግብት ይጠቁማሉ ።በጎዕዝ የተፃፉ አበዛኛወቹ መፃህፍት ሀይማኖታዊ ይዘት ያላቸዉ ቢሆኑም የመካከለኛዉ ዘመን ስልጣኔን የሚሳያሳዩ የተለያዩ የስነፅሁፍ፣ የፍልስፍና፤ የህክምናና የስነከዋክብት መፃህፍትም በዚሁ ቋንቋ እንደሚገኙ የዘርፉ ተመራማሪወች ይገልፃሉ። በመሆኑም የመካከለኛዉን ዘመን ታሪክ ለሚያጠኑ ተመራማሪወች አሁን አሁን ቀልብ እየሳበ የመጣ ይመስላል።
በቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ በታሪክ ትምህር ዘርፍ ዶክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ እንደሚናገሩት በቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ የቅርብና የመካከለኛዉ ዘመን ስልጣኔ ትምህርት ክፍል ስር በጎርጎሮሳዊዉ ዘመን ቀመር ከጥር 2017 ጀምሮ የግዕዝ ቋንቋ መስጠት ይጀምራል ።በትምህርት ክፍሉ ከአሁን ቀደም አረብኛና ዕብራይስጥን የመሳሰሉ የሴም ቋንቋወች እየተሰጡ መሆናቸዉን ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ ተናግረዋል።
«ግዕዝ የኢትዮጵያ ጥንታዊ የቤተክርስቲያን ቋንቋ ብቻ አይደለም ። ከአረብኛና ከዕብራይስጥ ጋር ዝምድና ያለዉ አስፈላጊ ቋንቋ ነዉ።
ይህንን ቋንቋ የሚያስተምሩ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ የቅርብና የመካከለኛዉ ምስራቅ ስልጣኔ ትምህርt ክፍል ሰወች አረብኛና ዕብራይስጥም ያስተምራሉ።»
በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ምርምር ያካሄዱት ፕሮፌሰር ማይክል ግሬቨርስ፤ ላቲን በአዉሮፓ ባህልና ቋንቋ ላይ ያለዉን ተፅኖ ያህል ግዕዝም በምስራቅ አፍሪካ ታሪክ ላይ ተፅዕኖ አለዉ ብለዋል። ምንም እንኳ ቋንቋዉ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስቲያን ዉጭ ተግባቦት ላይ እየዋለ ባይሆንም ፣በቋንቋዉ የተፃፉ የመካከለኛዉ ዘመን የሜዲተራኒያንን ታሪክና ስልጣኔ የሚያሳዩ በርካታ ፅሁፎች እንደሚገኙ ገልፀዋል።
« ግዕዝ ቋንቋ የተፃፉ በግዕዝ ብቻ የምናገኛቸዉ ፅሁፎች አሉ። በቀደመዉ ዘመን ወደ ግዕዝ የተተረጎሙ ነገር ግን መሰረታቸዉ የሜዲተራንያኑ አለም የሆኑ የጠፉና በጭራሽ ሊገጉ የማይችሉ ፅሁፎችም አሉ ። እነዚህን ፅሁፎች ለማግኘት ከኢትዮጵያ በስተቀር ሌላ አማራጭ የለም።»
ይሁን እንጅ ግዕዝን ማጥናት በቋንቋዉ የተፃፉ የ2000 አመት እድሜ ያላቸዉን በርካታ ፅሁፎች ላይ ምርምርና ጥናትን ለማድረግ እድል የሚሰጥና ለታሪክ ምርምር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።ይሁን እንጅ ቋንቋዉ ያለዉን ጠቀሜታ ያህል ትኩረት አልተሰጠዉም ። በመሆኑም የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ ይህንን የጥናት ተቋም በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል የማድረግ አላማ እንዳለዉ ጨምረዉ ገልፀዋል።
«በተለየ ሁኔታ ተስፋ የምናደርገዉ እዚህ ቶሮንቶ የከፈትነዉ። የጥናት ተቋም ወደፊት በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል እንዲሆን ነዉ። ያ ነዉ የእኛ አላማ።»
ለጥናት ተቋሙ በካናዳ የሚገኙ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በተለይ ዘ ዊክ ኤንድ በሚባል ቅፅል ስሙ የሚታወቀዉ ድምፃዊ አቤል ተስፋየ በግሉ 50 ሺህ የካናዳ ዶላር ማበርከቱ ታዉቋል።
በጀርመን ሃገር ሃምቡርግ ዩንቨርሲቲ በኢትዮጵያ ጥናቶች ትምህርት ክፍል እየተሰጠ የሚገኘዉ የግዕዝ ቋንቋ፣ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ዉጭ ያለ ሁለተኛዉ ግዕዝን የሚያስተምር ተቋም ይሆናል።
ፀሐይ ጫኔ
አዜብ ታደሰ