በ 3 03 2004 ዓ.ም. ሪፓርተር ጋዜጣ ላይ የወጣ
በኦሮሚያ ክልል ጉጂና ቦረና ዞኖች ውስጥ የሚኖረው አንድ ጎሳ ትክክለኛው መጠሪያ ስሜ ‹‹ዋዩ›› እንጂ ‹‹ዋታ›› ስላልሆነ ይስተካከልልኝ ሲል አቤቱታውን ለክልሉ ፕሬዚዳንት ቢሮ አቀረበ፡፡ አዲስ አበባ በመገኘት አቤቱታውን በግንባር ያቀረቡት የጎሳው ዐሥራ አንድ ተወካዮች ናቸው፡፡ ተወካዮቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በጉጂና ቦረና ዞኖች የሚገኘው ጎሳው ኦርጂናል መጠርያው ዋዩ ሆኖ ሳለ፣ ባለፈው ገዢ መደብ የመከፋፈል ሥርዓት ‹‹ዋታ›› በሚል ስያሜ ሲጠራ ኖሯል፡፡ ‹‹ዋታ›› መጥፎ ትርጉም ያለው ከሌብነት፣ ከአደን፣ ከስድብ ከዝቅተኛነት ጋር የተያያዘ በመሆኑ አስነዋሪው ስም እንዲቀየር ባለፉት 16 ዓመታት ጥረት መደረጉን ከተወካዮቹ አንዱ የሆኑት አቶ ጎዳና ጡና ተናግረዋል፡፡